Blog
የኢየሱስ ክርስቶስ ነኝ ፤ ሌላ የማንም አይደለሁም ፤ የፈጠረኝ እርሱ ፣ ያዳነኝ እርሱ ፣ የመጣልኝ እርሱ ፣ የተገረፈልኝ ፣ የተቸነከረልኝ ፣ እርቃን የታየልኝ ፣ ደሙን ያፈሰሰልኝ እርሱ ፣ የሞተልኝ ፣ በመቃብር ያደረልኝ ፣ የተነሳልኝ ፣ ያረገልኝ እርሱ ፣ በሰማይ ያለ ሊቀ ካህኔ እርሱ ፣ ዋሴ ጠበቃዬ መካከለኛዬ አስታራቂዬ ፣ መጥቶ የሚወስደኝ እርሱ፣ ሁሉ በጌታዬ ተጠናቆልኛል የኔ አባት ጀግና ነው በሁለንተናው ለእኔ ብቻ ሳይሆን ለአለም በቂ እና ከበቂ በላይ በላይ ነው አዳኝ ነው ብቻውን። ኃጢአተኞችን ሊያድን ክርስቶስ ኢየሱስ ወደ ዓለም መጣ የሚለው ቃል የታመነና ሁሉ እንዲቀበሉት የተገባ ነው(1ኛ ወደ ጢሞቴዎስ 1: 15) ።
ሲፈጥረኝ ብቻውን ነው የፈጠረኝ የሰው እርዳታ አላስፈለገውም ፣ ሲያድነኝም ብቻውን ነው ያዳነኝ ወይ ችንካሩን ወይም ግርፋቱን ያገዘው የለም። አልቀላውጥም እኔን ለማዳን አባቴ ብቻውን ብቁ ስለሆነ ተጨማሪ የመዳኛ መንገድ ፍለጋ አልቀላውጥም። ያውም ቅልውጥና አያጠግብም እኮ አያረካም እኮ ከእዛ እዚህ ከእዚ እዛ ያስብላል ቅልውጥና የዘወትር ምግብ አይሆንም ቅልውጥና እረፍት የለውም ።
ኑ እና በዚህ ጌታ እርፍፍፍፍፍፍ በሉ ካዳናችሁ ጌታ ጋር አዲስ ኪዳን ይኑራችሁ አዲስ ሕይወት ጀምሩ አሮጌውን ጥላችሁ ያማረውን ነጩን ልብስ የማያረጅ የማያድፈውን ዘለአለማዊ የጽድቅ ልብሳችሁን ልበሱ። የማትቀሙትን ፀጋ የማታጡትን እረፍት የማያሳዝነውን ደስታ የማይጠፋውን ሰላም የማይደበዝዘውን የቅድስና ብርሃን በስፍራ እና በቦታ ያልተገደበውን ከሞት በኋላ ላለን ሕይወት አስተማማኝ ዋስትና የሆነውን ፤ ከኃጢአት እና ከሲዖል የሚያድን ፣ ደግሞ ከጨለማ እና ከኩነኔ የሚታደግ የእግዚአብሔር ልጅ ኢየሱስ ክርስቶስ በደጃችሁ ቆሟል .. አዲሱን ኪዳን ከእርሱ ጋር አድርጉ።
ዓለም እረፍት አልሰጠችኝም ፣ ብዙ አይነት ሃሳቦችን እና እምነቶችን እከተላለሁ ከሞት በኋላ ግን የት እንደምሄድ አላውቅም እያላችሁ የሞታችሁን ቀን በፍርሃት እያሰባችሁ ምትኖሩ ፣ ከሞት በኋላ የእግዚአብሔር እቅፍ ሳይሆን ሲዖል የሚታያችሁ ፣ እያደረጋችሁ ባላችሁት ኃጢአት ሕሊናችሁ ሰላም አጥቶ ዘወትር ጠላት የሚከሳችሁ ፣መዳን እፈልጋለሁ ፣ መቅበዝበዝ ሰልችቶኛል የምትሉ ኑ የሚወዳችሁ ጌታ አለ ፤ ኑ ከዚህ ሁሉ የሚያስጥላችሁ አዳኝ ጌታ አለ ፣ በክንፎቹ ጥላ ስር ማደር ይሆንላችኋል ኢየሱስ ክርስቶስ ይወዳችኋል። ይህንን የቃል ኪዳን ፀሎት አምናችሁ አብረን እንፀልያለን ... በቅንጣት ሰከንድ ውስጥ የዘመናት ሸክማችሁን እግዚአብሔር ከላያችሁ ያንከባልላል።
እንፀልይ ..
እግዚአብሔር ሆይ አመሰግንሃለሁ ፤ አንድያ ልጅህን እኔን ለማዳን ወደ ምድር እንደላክኸው አምናለሁ ፤ ከኃጢአት እና ከዘለአለም ሞት ሊያድነኝ ልጅህ ኢየሱስ ክርስቶስ ስለ እኔ እንደተሰቀለ እንደሞተ አምናለሁ ፤ እኔን ስለማፅደቅም በሶስተኛው ቀን ከሞት እንደተነሳ አምናለሁ ፤ ወደ አንተ ወደ አባቱ ስፍራን ሊያዘጋጅልኝ እንደሄደ ዳግመኛም እርሱ ወዳለበት ሊወስደኝ እንደሚመጣ አምናለሁ፤ ዓለምን እክዳለሁ ፣ ሰይጣንን እክዳለሁ ፣ ዛሬ እውነትና መንገድ ሕይወትም በሆነው በአንድ ልጅህ በኢየሱስ ክርስቶስ ወደ አንተ እቀርባለሁ ፣ የልጅህ የኢየሱስ ክርስቶስ ደም ከኃጢአቴ ሁሉ ያንፃኝ፣ አንተ አባቴ ነህ ልጅህ ስላደረግኸኝ አመሰግንሃለሁ። ከእንግዲህ ወዲህ ያንተ ነኝ ፣ በስራዬ ሳይሆን በልጅህ በኢየሱስ ክርስቶስ ስራ ምክንያት በቀኝህ ስላስቀመጥከኝ አመሰግንሃለሁ ። ዛሬ ከቅዱስ መንፈስህ ስለተወለድኩ አመሰግንሃለሁ። በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አሜን።

የቅርብ ቀን አስተያየቶች :

  • ESHET

    1208 days ago

    የጌታ ስራ ይብዛልህ 🙏



Related Posts


Leave for a comment


  • Latest posts


  • ያለፍከው !


    post-img

    እግዚአብሔር ውለታ ሊውልልህ ሲፈልግ ሰዎች በማያወቁት ሸለቆ ያሳልፍሃል። ወንድሞችህ በጭካኔ አንተን ገፍትረውህ የጣሉበትን ጉድጓድ ጥልቀቱን እንኳን አያውቁትም ።

    311 days ago
  • ያለፍከው !


    post-img

    እግዚአብሔር ውለታ ሊውልልህ ሲፈልግ ሰዎች በማያወቁት ሸለቆ ያሳልፍሃል።

    311 days ago
  • ያለፍከው !


    post-img

    ሌሎች የሠጠሙበትን ማዕበል አንተ የተሻገርከው አስተዋይ ስለሆንክ ሳይሆን ጌታ ስለ ራራልህ ነው።

    1343 days ago
  • የጫካ ዜጎች


    post-img

    በአንድ ጫካ ውስጥ አንድ ከሺ ዓመታት በላይ እድሜ የጠገበ ዋርካ ነበረ፡፡ ዋርካው እጅግ ሰፊ፣ ውስብስብና ታላቅ ነው፡፡ በላዩ ላይ አዕዋፍ፣ በሥሩም እንስሳት ይጠለሉ ነበር፡፡ ከፊሉ ፍሬውን ከፊሉም ቅጠሉን ይመገባሉ፡፡ ሌሎቹም ግንዱንና ሥሩን ፍቀው ይበላሉ፡፡ አንዳቸው ለሌላቸው እንስሳትና አዕዋፍ የጠቀሙበት፣ አንዳቸውም አንዳቸውን የበሉበት ዘመን ነበር፡፡ አንዳቸው ከአንዳቸው ጋር የሚጋቡበት፣ አንዳቸውም ከሌላቸው ጋር የሚዋጉበት ዘመን አለ፡፡ ፈረስና አሞራ ተጋብቶ ክንፍ ያለው ፈረስ ተወልዶ ነበር አሉ፡፡ ታላላቆቹ እንስሳት በልተዋቸው ዘራቸው የጠፉ እንስሳትም አሉ፡፡

    1683 days ago